Tuesday, June 23, 2020

ተረት

ተረት ልነግራቹ ነው፡፡ በጥሞና አድምጡኝ፡፡

ተረት ተረት፡፡

የመሠረት አላችሁ፡፡

ጥሩ! ተረቱን እንደሚከተለው እተርካለሁ፡፡

በሆነ ጊዜ የሆነ ቦታ ሚስቱን በጥርጣሬ የሚከታተል አንድ ባል ነበረ፡፡ ከዕለታት በአንዱ ቀንም ውሽማዋ ከቤቱ ሲወጣ ተመለከተና ዛሬማ የእጁን እሰጠዋለሁ ብሎ ሽመል ይዞ ተከተለው፡፡ ከቆይታ በኋላ ባዶ እጁን ወደቤቱ ተመለሰ፡፡ ሚስቱ ማጀት ውስጥ ነበረችና
“ስሚ አንቺ!” ብሎ ተጣራ፡፡
“እነሆኝ” ስትል መለሰችለት፡፡
“ያ ውሽማሽ እኮ ደበደበኝ”፡፡
“በምን?” ብላ ጠየቀችው፡፡
“በሽመል” ብሎ መለሰላት፡፡
“ሽመል መያዝ አልለመደበትም ነበር፤ ዛሬ እንዴት ይዞ ወጣ?” አሁንም ጠየቀች፡፡
“እሱማ ሽመል መያዝን ከየታባቱ ያውቅና! የእኔን ሽመል ቀምቶ ነው እንጂ የመታኝ” ሲል መለሰላት፡፡

ተረቴን መልሱ፤ አፌን በዳቦ አብሱ!

1 comment:

Anonymous said...

Great Idea!

 እኔ የማወራት የእርሷ ጆሮ ሲደርስ መልኩን እየሳተ እየተቀየረ፣ ከማፋቀር ይልቅ እኛን ከማዋደድ ጥል ፈጣሪ ኾነን እያጠራጠረ፡፡