Monday, October 8, 2018

ወዴት ዘመም ዘመም!


አቶ ልደቱ አያሌው ከዋልታ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉት የሁለት ክፍል ቆይታ ተመለከትኩት፡፡ ሆኖም ግን ከቆይታቸው የተረዳሁት ነገር እስከዛሬ የሚነገርባቸውን የሚያጠናክርልኝ እንጂ ንጹህነታቸውን የሚያሳይ ሆኖ አላገኘሁትም፡፡ በተደጋጋሚ የሚያቀርቧቸው ክስ እንበላቸው ወቀሳዎች እርስ በርሳቸው የሚጣረሱ ናቸው፡፡ አንዴ የተሻልሁ ፖለቲከኛ በመሆኔና በምክንያትነቴ ተገለልኩ፤ ሐሰተኛ ውንጀላ ተበራከተብኝ ሲሉ ቆይተው ሌላ ጊዜ ደግሞ በማንነቴ የፓርቲ ስልጣን እንዳላገኝ ተደረግሁ፣ የሻጥር ዘመቻ ተዘመተብኝ ይላሉ፡፡ በማንነቴ ሲሉም ዐማራ በመሆኔ ማለታቸው ይመስለኛል፡፡

ዐማራ በመሀኔ መገለል ደረሰብኝ የሚሉት ሰው ግን ለዐማራ ሕዝብ መብት ለመከራከር ከተቋቋመው መ.ዐ.ሕ.ድ አፈንግጠው ወጥተው የራሳቸውን ድርጅት የመሠረቱትና በፖለቲካ ውስጥ በነበሩባቸው ከ20 በላይ ዓመታት ውስጥ ዐማራው ፍዳውን ሲያይ ድምጻቸውን አጥፍተው ሲመለከቱ እና አንዳንዴም በአደባባይ ሲያሽቃብጡ ይታዩ የነበሩት ሰውዬ መሆናቸው ይገርማል፡፡ ታዲያ በማንነታቸው የሚናገሩት ሁሉ ከደረሰባቸው እስከዚህ ጊዜ ድረስ ምን አስጠበቃቸው? ለምንድን ነው ባለፉት 13 ዓመታት ውስጥ ትንፍሽ አላሉም? ስንቶቹ ዐማራ በመሆናቸው ብቻ ብዙ ስቃዮችን ሲሰቃዩ ድምጻቸውን አጥፍተው ጎሬ ውስጥ ተወሽቀው የኖሩት? ዛሬስ ድንገት ዐማራ በመሆኔ ተበድያለሁ ላመለት የሚያበቃቸው ምን ነገር አገኙ? ነው ወይስ ከአቶ መለስ ጀምሮ ሲለለምኑኝ ነበር ያሉትን ጥያቄ ተቀብለው የቀድሞው ብ.አ.ዴ.ን (የዛሬው አ.ዴ.ፓ) አባል ለመሆን ወሰኑ? ወይስ አ.ብ.ንን (የዐማራ ብሔርተኝነት ንቅናቄ) ለመቀላለቀል ዕድሉን አገኙ? ይህ ሆኖ ከሆነ ሰውዬው በሕይቀት ዘመናቸው ዐራተኛ ፓርቲያቸውን ተቀላቅለው የማውደም ዓላማቸውን ለማሳካት እየቋመጡ ያሉ ይመስለኛል፡፡

No comments:

 እኔ የማወራት የእርሷ ጆሮ ሲደርስ መልኩን እየሳተ እየተቀየረ፣ ከማፋቀር ይልቅ እኛን ከማዋደድ ጥል ፈጣሪ ኾነን እያጠራጠረ፡፡