የሆነ የአገራችን ጫፍ ላይ ከጎረቤት አገር የመጡ ታጣቂዎች ጥቃት ሲያደርሱ ኃላፊነት ወስዶ ተመጣጣኝ እርምጃ የሚወስደው አሊያም ከታጣቂዎቹ አገር መንግሥት ጋር በመደራደር እርምጃ የማስወሰድ እና ለተበዳዮችም ካሳ የማስከፈል ኃላፊኀቱ ግን የማን ነው? የፌደራሉ መንግሥት፣ የክልል መንግሥታት ወይስ የአካባቢው ጎሳ አለቆች? 140 ዜጎቹ አልቀው ወንበዴ ምናምን እያለ የሚቀባጥረው ግን መንግሥታችን ነው የሚባለው? ማንኛውም (አምባገነንነት እስካፍንጫው የወጣበትም) መንግሥት የሚገዛው ምድር ሰዎች ሲደፈሩ የደፈሯቸውን ይቀጣል፡፡ መቅጣት ካልቻለ እንኳን ዓለም አቀፍ ፍትህ የሚገኝበትን መንገድ ይፈልጋል፡፡ ዜጎቹን ራሱ ቢበድላቸውም ሌላ እንዲነካቸው ግን አይፈቅድም፡፡ የኛው ግን እንደ ዩግሌና መደብ አልባ ገዢ ሆኖ ነው መሰል ራሱ በድሎ ለሌላውም እያሳለፈ እየሰጠን ነው፡፡
በ#ጋምቤላ የደረሰው ጥቃት የጋምቤላ ብቻ ጥቃት አይደለም፡፡ 100, 000, 000 ሰዎች ናቸው የተጠቁት፡፡ የነሱ መንግሥት ተብየውም ነው የተናቀው፡፡
የተናቀ መንግሥትን ያህል የሚያሸማቅቅ ግን ምን አለ?
በ#ጋምቤላ የደረሰው ጥቃት የጋምቤላ ብቻ ጥቃት አይደለም፡፡ 100, 000, 000 ሰዎች ናቸው የተጠቁት፡፡ የነሱ መንግሥት ተብየውም ነው የተናቀው፡፡
የተናቀ መንግሥትን ያህል የሚያሸማቅቅ ግን ምን አለ?
No comments:
Post a Comment