Saturday, April 16, 2016

ተስፋ የለሽ መንግሥት

የሆነ የአገራችን ጫፍ ላይ ከጎረቤት አገር የመጡ ታጣቂዎች ጥቃት ሲያደርሱ ኃላፊነት ወስዶ ተመጣጣኝ እርምጃ የሚወስደው አሊያም ከታጣቂዎቹ አገር መንግሥት ጋር በመደራደር እርምጃ የማስወሰድ እና ለተበዳዮችም ካሳ የማስከፈል ኃላፊኀቱ ግን የማን ነው? የፌደራሉ መንግሥት፣ የክልል መንግሥታት ወይስ የአካባቢው ጎሳ አለቆች? 140 ዜጎቹ አልቀው ወንበዴ ምናምን እያለ የሚቀባጥረው ግን መንግሥታችን ነው የሚባለው? ማንኛውም (አምባገነንነት እስካፍንጫው የወጣበትም) መንግሥት የሚገዛው ምድር ሰዎች ሲደፈሩ የደፈሯቸውን ይቀጣል፡፡ መቅጣት ካልቻለ እንኳን ዓለም አቀፍ ፍትህ የሚገኝበትን መንገድ ይፈልጋል፡፡ ዜጎቹን ራሱ ቢበድላቸውም ሌላ እንዲነካቸው ግን አይፈቅድም፡፡ የኛው ግን እንደ ዩግሌና መደብ አልባ ገዢ ሆኖ ነው መሰል ራሱ በድሎ ለሌላውም እያሳለፈ እየሰጠን ነው፡፡
በ#ጋምቤላ የደረሰው ጥቃት የጋምቤላ ብቻ ጥቃት አይደለም፡፡ 100, 000, 000 ሰዎች ናቸው የተጠቁት፡፡ የነሱ መንግሥት ተብየውም ነው የተናቀው፡፡
የተናቀ መንግሥትን ያህል የሚያሸማቅቅ ግን ምን አለ?

No comments:

 እኔ የማወራት የእርሷ ጆሮ ሲደርስ መልኩን እየሳተ እየተቀየረ፣ ከማፋቀር ይልቅ እኛን ከማዋደድ ጥል ፈጣሪ ኾነን እያጠራጠረ፡፡