ዛሬ በአንተ ዘመን አድጎ ተመንድጎ ስለተለወጠ የሰው ልጅ እውቀቱ፣
ጊዜው
ስላለፈ ዐለምን ለማወቅ መልፋት መዳከሩ መጽሐፍ መጎተቱ፣
ማሰብ
ማሰላሰል፣ መጠየቅ መመርመር ጊዜ እያባከኑ፣
ዝና ‘ማያስገኙ
ሐብት አያከማቹ ገንዘብ እየሆኑ፣
ፋሽኑ
አልፎባቸው ርቋቸው ሔዶ ጥሏቸው ዘመኑ፣
የሊቅነት
ልኩ የአዋቂነት ሚዛን ድፍረት በመሆኑ፣
እውቅና
ቀርቶብህ ሹመት እና ዝና፣
ሲያጓጓህ
እንዳይኖር መባል የኛ ጀግና፣
ፍለጋህን
ትተህ ማሠሡን ብራና፣
ጥያቄ
መጠየቅ ሙግትን እርሳና፣
ምን ይሉኝን
ንቀህ ጆሮህን ዝጋና፣
ማየት
ማመዛዘን ይህ ቢሆን እንዲያ ነው … ማለትን በአንድምታ፣
አራግፈህ
ውጣና በምላስህ ከብረህ ትገዛለህ እና ሊቅነትን በአፍታ፣
ውጣ በአደባባይ
ማንንም ሳትሰማ ፎክር እና ደንፋ፣
ተጀነን
ተንጠርበብ፤ ኮራ ብለህ ተጓዝ ደረትህን ንፋ፣
በዝና
ላይ ዝና ክብር እየሰለመህ የምትነዳው ጭፍራ፣
የእውቀትህ
ምሥክር ገድልህን ዘርዛሪ ብዙ እንድታፈራ፣
በየአደባባዩ፣
በየቴሊቪዥኑ እንዳሸን በፈላው ተንጎራደድ ወጥተህ በየተራ፣
ስትፈልግ
ጩህበት፣ ሲያሻህ ስደብበት በልበ ሙሉነት ማንንም ሳትፈራ፣
ታግለህ
ተሰውተህ፣ ያገኘኸው ስኬት ድልህ ስለሆነ፣
አፍን
አስከፍቶ ድርሳንን ያዘጋ፤ መዝገብ ያስከደነ፡፡