Saturday, May 25, 2024

 እኔ የማወራት የእርሷ ጆሮ ሲደርስ መልኩን እየሳተ እየተቀየረ፣

ከማፋቀር ይልቅ እኛን ከማዋደድ ጥል ፈጣሪ ኾነን እያጠራጠረ፡፡

Sunday, October 29, 2023

እኛ

 ዐመት እየጠበቅን ደምቀን እንውላለን፣

ሐዘን ለቆን ሳይሆን ተስፋን እያስቀደምን።

Monday, September 18, 2023

አይቀርም ተኝቶ

 እንኳን ነፋስ መንፈስ

ውቅያኖስ ቢመጣ በመዓበል ታጀቦ
ውሽንፍሩን ይዞ ወጀብ አሰክተሎ፤
መውደዱን ረግጦት አፈርን አልብሶ
ሌላ የሚያስገባ በር ሰጥቶ ለጀቦ
ድፍን ልብ የለኝም የሚቀር ተታልሎ፡፡
All reactions:

Friday, July 16, 2021

ከወዴት ሊመጣ …?


ገና በማለዳ ለማኙ ሳያ* ወፍም ሳይንጫጫ ቀድሞ ከንጋቱ፣
ነቅቶ የሚያነቃን ውርጭ ሳይቆልፈው ስል ሆኖ አንደበቱ፣
“ማን ይሆን ዘነድሮን የሚገኘው አልፎ፤
ከመዓት ከመከራው ከመቅሰፍቱ ተርፎ”
እያንጎራጎረ ሲያዜም እየሰማን ከንፈር እየመጠጥን፣
ሥም ያወጣንለት መጠሪያ ‘ሚሆነው “እብድ ወፈፌ” ብለን፣
መንጋቱ ‘ሚታወቅ ሰማይ መገለጡ ጨለማው ማለፉ፣
በእሱው ዜማ ነበር ሁሌ ‘ሚታወጁ ሰርክ የሚለፈፉ፣
በእሱ እንዳልነበረ ደምቆ የምናየው ተውቦ መንገዱ፣
የተሳለቅንበት ጆሮ የነሳነው የምንለው እብዱ፤
ዛሬ፡-
በተራችን ሁላችንም አብደን ሲጠፋብን መላ፣
እህል እየጠጣን ውኃ ልናላምጥ አኝከን ልንበላ፣
ነፋስም ልንጨብጥ ስናባዝን ስንለፋ፣
ውቅያኖስን ልንጠልቅ ጨርሰን በጭልፋ፣
ዳናው ቢናፍቀን ቢያምረን እንጉርጉሮው፣
ማን አየሁ ሊለን ምን ጅብ እንደበላው?
እናማ
ዜማውን ተውሰን ሥንኝ አሰናኝተን፣
እንዲህ ያለ ለቅሶ እንጉርጉሮ አወጣን፣
ዛሬስ ወዴት ገብቶ ምን ጅብ ቢውጠው ነው ዳናውን ያጠፋ፣
አፋችንን ሆኖ የማይናገረው ምን ሆነን እንዲያይ ነው ካሁኑ የከፋ፣
“ማን ይሆን …” እያለ አይናገር ምነው የማይጮኸው ዛሬ፣
ግድግዳው ተንዶ መጠጊያ ስናጣ ስንከበብ በአውሬ፣

 እኔ የማወራት የእርሷ ጆሮ ሲደርስ መልኩን እየሳተ እየተቀየረ፣ ከማፋቀር ይልቅ እኛን ከማዋደድ ጥል ፈጣሪ ኾነን እያጠራጠረ፡፡