Friday, July 16, 2021
ከወዴት ሊመጣ …?
Thursday, December 24, 2020
Sunday, November 1, 2020
Monday, October 12, 2020
Saturday, October 3, 2020
Thursday, August 27, 2020
ማንም ነህ ምንም ነህ (2)
ምናምኒት ነገር እጅህ ላይ ባይገኝ ብታጣ ብትነጣ፣
እሳት
ተለቅቆብህ ከቤት ብትሳደድ ሜዳ ብትሰጣ፣
አዝመራህም
ነድዶ ጨገሬታ ጠፍቶ ጠኔህም ቢበዛ፣
ዕድል
ፊት ብተነሳህ አሳዳጅ የሚሆን ተላትህን ብትገዛ፣
አይክፋህ ወንድሜ፣
በደል አይሰማህ መገፋት መጣልህ ፈፅሞ አያስከፋህ፤
ምክንያቱም፣
አንተ ማለት ለዓለም "ምንም ነህ ማንም ነህ"።
ወገኔ ነው ያልኸው እምነት
ጥለህበት ያደረግኸው ተስፋ፣
ቢሸሽ ቢሸሸግም ርቆ እየሔደ
ካይንህ ተተሰውሮ ከጎንህ ቢጠፋ፣
ጊዜ እየታከከ ጉልበት ቢያጎለብት
ለውድቀትህ ቢቆም አንተኑ ሊገፋ፣
ብንን ብሎ ቢሔድ ነፋስ
እንደገፋው እንደጉም ቀሎ የጣልህበት ተስፋ፣
አይክፋህ ወንድሜ፣
በደል አይሰማህ መገፋት መጣልህ ፈፅሞ አያስከፋህ፤
ምክንያቱም፣
አንተ ማለት ለዓለም "ምንም ነህ ማንም ነህ"።
የምትገብርለት
ዓመት እየጠበቅህ፣
ቆሜያለሁ
የሚልህ አንተን ልጠብቅህ፣
ካጥቂዎችህ
ቢያብር ደጋግሞ ቢክድህ፣
ዓለም ስለተወህ ዓለም ስለረሳህ፣
አይክፋህ ወንድሜ በደል አይሰማህ፣
ይልቅስ፣
ቅስምህን አበርታ
መንፈስህን አጽና፣
ቀበቶህን አጥብቅ
አንገትህንም አቅና፣
አንተን የሚታደግ
አውጪ ከፈተና፣
ከራሥህ በስተቀር
ማንም የለምና፤
አልያማ፣
ጥረህ ተጣጥረህ ታግለህ
ካላሸነፍህ ካልወጣህ አርነት፣
ዝምታህ ብርታቱ መታገስህ
ኃይል ሆኖት ጉልበት፣
ሽህ ምንተሸህ ሆኖ
ተንጋግቶ ይመጣል፣
የቅስምህ መሰበር
ውስጡን ወኔ ሞልቶት፣
ኪሱን ሊያደላድል
ሊሞላው የሱን ቤት፣
ትርፉን እያሰላ ሊሸጥ
ያንተን ሕይወት፣
ምክንያቱም፣
ራሥህ ለራሥህ መድኃኒት
ካልሆንኸው መንፈስህ በርትቶ፣
ደድረህ ካልመከትህ
ኃይልህ ተጠራቅሞ ቅስምህም ጎልብቶ፣
ዓለም አይሰማህም
ደራሽም የለህም፣
የሚገፋህ እንጂ
ደጋፊ አታገኝም፡፡
Wednesday, August 19, 2020
መንገዴን አሳይኝ
ገና ከጅምሩ፣
አንቺ ስትመሪ ስከተልሽ ኖሬ፣
ፍቅር በተባለ ገመድሽ ታስሬ፣
ያመጣኝን መንገድ ዛሬ ሳየው ዞሬ፣
ወከክ ብየ ቀረሁ አንገቴን ሰብሬ፤
መቼስ ለምን ካልሽኝ፡-
አንቺ አንቺን እያለ ተከትሎሽ እግሬ በመንደፋደፉ፣
ተስቦ ተገፍቶ አቀበቱን ወጥቶ ሲደርስ ከአፋፉ፣
በግልምጫሽ ብቻ ልቤ ሲደነግጥ ግፍፍ ሲል ቀልቡ፣
ወኔ እና ተስፋዬ በነፋስ ሽውታ ተንነው ገደል ገቡ፤
እናም፣
መውደድ እና ፍቅር ብርታት እየሰጡ እያሉኝ በል ግፋ፣
የወጣሁት ዳገት ወኔን ተመርኩዤ ታጅቤ በተስፋ፣
መልሶ ለመውረድ ጭንቅ ጥብ ሆኖብኝ የበረታ ዳፋ፣
ቁልቁል ተንደርድሬ ባናቴ እንዳልል ትክል ሔጄ እንዳልደፋ፣
ከተነሳሁበት መልሶ የሚያደርስ መሹለኪያ የሚሆን ከማጥ የሚያወጣ፣
መንገድ ምሪኝ እና ጭንቄን ልገላገል ካስገባሽኝ ዓለም ከሰመመን
ልውጣ፡፡
እኔ የማወራት የእርሷ ጆሮ ሲደርስ መልኩን እየሳተ እየተቀየረ፣ ከማፋቀር ይልቅ እኛን ከማዋደድ ጥል ፈጣሪ ኾነን እያጠራጠረ፡፡
-
በድንቅ ተጋድሎ አሻራ ያኖረ፣ በሑባሬ ገመድ ሐገርን ያሰረ፡፡ ማረሻና ድግር፣ ሞፈርና ቀንበር ተሸክሞ ወጥቶ የሚታገል ካፈር ማጭድና መንሹን ማርገቢያ ላይዳ ችግሩን ሸክፎ ከትቶ በአኩፋዳ ጋራው...
-
ያለፉት ዐርባ አምስት (45) ዓመታት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በመጠላለፍና ጣት መቀሳሰር የተሞላ እንደነበርና እንደሆነ የሚያሳዩን በርካታ ማስረጃዎች አሉ፡፡ ይህም በዛሬው ትውልድ ላይ የቀረውን ጠባሳ ሰፊ እንዲሆንና ዐዲ...
-
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን የጉዞውን መነሻ በ19 ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ብቅ ባሉት ጋዜጣዎች ጀምሮ በዓይነት እና በቁጥር እየሰፋ ዛሬ ላይ ያለበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ጋዜጣ ምዕት ዓመት የሞላው ሲሆን የመጀመሪያው ሬዲ...