Sunday, November 27, 2016

ጥሩ መጽሐፍ ማንበብ

መጻሕፍት ጥሩ ሆነው ሲቀርቡ አእምሮን ያድሳሉ፡፡ የንባብ ፍላጎትን ከተወሸቀበት ሥርቻ  መንጥቀው ያወጡታል፡፡ በተለይማ በሕይወት ልምድ ታጅበው ሲቀርቡልን፡፡
የፕሮፈሰር ሽብሩ ተድላ "ከጉሬዛም ማርያም እስከ አዲስ አበባ፤ የሕይወት ጉዞና ትዝታየ" ምንም ዓይነት የተደበተ ስሜት ውስጥ ቢሆኑ የሚኮረኩር ነው፡፡ ከታሪካዊ መረጃዎች ሐብታምነቱ እስከ ባሕል መገለጫነቱ ይህ ነው በሚባል ዋጋ ሊተመን የሚችል አይደለም፡፡ ከኢትዮጵያ ማዕከላዊ አካባቢ ማኅበረሰብ አንዱ ከሆነው ከጎጃም ማኅበረሰብ ለማትተዋወቁ ያስተዋውቃችኋል፤ ለምትተዋወቁ ትውውቃችሁን ያደረጃል፡፡ ላደጋችሁበት ደግሞ የትዝታ መቆስቀሻ ይሆናልና አንብቡት፡፡

 እኔ የማወራት የእርሷ ጆሮ ሲደርስ መልኩን እየሳተ እየተቀየረ፣ ከማፋቀር ይልቅ እኛን ከማዋደድ ጥል ፈጣሪ ኾነን እያጠራጠረ፡፡