Wednesday, April 8, 2015
Ethiopia-@-Glance: Introducing Ethiopia
Ethiopia-@-Glance: Introducing Ethiopia: Ethiopia has a diverse mix of ethnic and linguistic backgrounds. It is a country with more than 80 different ethnic groups each with its ow...
Friday, April 3, 2015
ከፀሐይ በስተጀርባ
ከፀሐይ በስተጀርባ
ፀሐይ እየወጣች ነው፡፡ የተደበቀው ጉድፍ ሁሉ በአደባባይ ይገለጣል፡፡ በየጥሻው የተወሸቀው ሁሉ ለሕዝብ ይታያል፡፡ ድምጽን
አጥፍቶ የተሠራው ሁሉ በከፍተኛ ድምጽ ይጮሃል፡፡ ረግቶ የነበረው ሁሉ በከፍተኛ ፍጥነት ይንቀሳቀሳል፡፡ አንቀላፍቶ የነበረው ከተማ
በድንገተኛ ትርምስ ይታጀባል፡፡ አቀርቅሮ የነበረው በረንዳ ሁሉ አንገቱን ቀና ያደርጋል፡፡
ገና በማለዳው ቢራ
እየጠጣሁ ነው፡፡ የሚያየኝ ሁሉ ‹‹በሰላም ነው እንዴ?›› እያለ ይጠይቀኛል፡፡ እኔ ለዓመታት ያደረግኩት ስለሆነ ምንም አይሰማኝም፡፡
ዛሬ ግን ከሰፈሬ ርቄ ነው የምጠጣው፡፡ ስድስት ኪሎን ለቅቄ ጎፋ ካምፕ ሔጃለሁ፡፡ እዚያ ማንም አያውቀኝም፤ ለምን ብሎ የሚጠይቀኝም
የለም፡፡ ማንኛውንም ነገር እንደፈለግኩ መፈጸም እችላለሁ፡፡
ሦስት ቢራ አጠናቅቄ
አራተኛውን አጋምሸዋለሁ፡፡ ሞቅታ እየተሰማኝ እንደሆነ ፊቴ ላይ ችፍ ባለው ላቭ ማወቅ ይቻላል፡፡ በምኖርበት ሰፈር ጨለማን ጠብቄ
የማደርገውን ዛሬ በብርሃን ለፈጸም ወሰንኩ፡፡ ሁለት ሴቶች በአንድ ላይ የተቀመጡ መሆናቸውን አየሁ፡፡ ያለምንም ማመንታት ተነስቼ
ወደነሱ ሔድኩ፡፡ ያለምንም ጥያቄ ተቀላቀልኳቸው፡፡ ፊታቸው ላይ የመደንገጥ ስሜት ባይታይም ለመቆጣት ሞከሩ፡፡ ‹‹ከደበራችሁ መነሳት
እችላለሁ›› አልኳቸው፡፡ ‹‹በል አርፈህ ተቀመጥ›› አለችኝ ጠቆርና ቀጠን ያለችው ልጅ፡፡
እድሜያቸው ከአሥራ
ስምንት ዓመት አያልፍም፡፡ ገና ሲታዩ የሚያሳሳ ውበት ተሸክመዋል፡፡ ተመሳሳይ ቀለም ያለው ለብሰው አንድ ዓይነት ቦርሳ ይዘዋል፡፡ ከቆዳ ቀለማቸው በስተቀር በማንኛውም
ነገር ተመሳሳይ ናቸው፡፡ ከአነጋገር እስከ አረማመዳቸው አንዷ የአንዷ ቅጅዎች ናቸው፡፡ እንዳየኋቸው መንትያዎች መሆናቸውን ነው
የገመትኩት፡፡ እናም የመጀመሪያ ጥያቄየ የሆነው ‹‹መንትዮች ናችሁ እንዴ?›› የሚለው ነበር፡፡
‹‹ሃ!ሃ! አነወመስልም?››
መለሰች ቀላ ብላ ወፈር ያለችው ሴት፡፡ ‹‹ስለመሰላችሁኝማ ነው የጠይቅኳችሁ›› አልኳት፡፡ ‹‹እሱን ቆይተን እንደርስበታለን፡፡
ይልቅ አሁን ምን ትጋብዘናለክ?›› አለችኝ፡፡
‹‹የሚጠጣ ነው?››
‹‹ሆ! ሆ! ኧረ ገና
ቁርስ አልበላንም፡፡ የሚበላ ነገር፡፡ …›› አለች፡፡
‹‹እናንተ የመረጣችሁት
ይሁና! መቸም እናንተን የመሰሉ የቆንጆ መለኪያዎች ጋር ተቀምጦ አልጋብዝም ማለት ውርደት ነው፡፡›› አልኳቸው፡፡ እንደ ድሮው ቢሆን
ኖሮ እንኳን እነሱን የምጋብዝበት የራሴን ቢራ የምጎነጭበት ሰባራ ሳንቲም እንኳን ሊኖረኝ አይችልም- ለዛውም በዛሬዋ ዕለት- የወሩ
መጨረሻ በቀረበባት በሃያ ሁለተኛዋ ቀን፡፡ እድሜ ለዚያ መላጣ ፈረንጅ፡፡ በሽዎች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ዘርግፎልኝ ሔዷል፡፡
ጠቆር ያለችው ሴት
አጨበጨበች፡፡ አስተናጋጁ የኋላ እግሩ እንደ ተሰበረ በሬ ሳብ ጉብ እያለ መጣ፡፡ ‹‹ምን ልታዘዝ?›› በሰለለ ድምጽ ጠየቀ፡፡ ‹‹የቤቱን ስፔሻል፡፡ … ደግሞ በጥሩ ሁኔታ ይሠራልን እሽ!››
ብላ በመብረቅ ዐይኗ ጠቅ አደረገችው፡፡ በደስታ ሰክሮ ‹‹ጥይት እንደሳተው›› እየተደናበረ ሔደ፡፡
‹‹ተጫዎት!›› አለች
ቀይነት ያላት፡፡
‹‹እየተጫዎትኩ ነው››
መለስኩ፡፡
‹‹ለደቂቃዎች አብረን ተቀመጥን፤ ነገር ግን እስካሁን አልተዋወቅንም፡፡ እሷ
ኤልሲ እኔ ደግሞ ሳሪ እንባላለን፡፡ አንተስ ማን ትባላለህ?››
‹‹እ! የኔ ስም እንኳን
ቢቀር ይሻላል፡፡ በጣም ረዥም እና ለመያዝም የሚያስቸግር ነው፡፡››
‹‹ማለት?››
‹‹የኔ ስም ከሦስት
መስመር ያልፋል፡፡ ዓለም ከኔ በፊት አይታው የማታውቅ ድንቅና ብርቅየ ስም ነው፡፡››
‹‹እውነት! እስኪ
ንገረንና እንስማዋ!››
(ይቀጥላል….)
Monday, January 5, 2015
ብቸኛ
ያምሃል አለኝ ገና እንዳገኘኝ፡፡ ምንም አልመለስኩለትም፡፡ ፊቴን
ቅጭም አድርጌ ዐይኖቼን አጥብቤ አየሁት፡፡ ውስጤን ዘልቆ ያየኝ እስኪመስለኝ አፈጠጠብኝ፡፡ ማመምማ አሞሃል፡፡ ጸበል ወይም ሀኪም
ቤት መሄድ ነበረብህ ማለት ጀመረ፡፡
አዎ አሞኛል፡፡ በጣም ነው የሚያመኝ፤ ስሟን እየጠራ የሚያስታውሰኝ ሰው በመጣ ቁጥር እታመማለሁ፡፡ ራሴን ነጻ አድርጌ ለመስራት እየጣርኩ ለውጥ ለማምጣት ደፋ ቀና እያልኩ የተሸለ ስራ መስራት እንደጀመርኩ አንዱ ያነሳታል፡፡ ያን ጊዜ የኔ ውስጥ ይናወጣል፡፡ ሁሉም ነገር ያመኛል፡፡ ስራ ያስጠላኛል፡፡ መተኛት ያምረኛል፡፡ እንቅልፍ ይጫጫነኛል፡፡
ስለዚህ በቃ ማንንም መግኘት የለብኝም፤ ሁሉም ሰዎች ጠላቶቼ ናቸው፡፡ የማልፈልገውን ነገር መረዳት እስካልቻሉና እኔን ለህመም እስከዳረጉ ድረስ የሰዎች ወዳጅነት ምኔም አይደለም፡፡ እነሱ ለኔ ጥሩ ከማሰብ እያሰረጉት ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም ግን የስሜቴን መለዋወጥ ተመልክተው ሊረዱ ይገባል፡፡ አለበለዚያ የእኔን ህይወት አደጋ ውስጥ የሚከት ማናቸውም ምክርና ሀሳባቸውን ይዘው በዚያው በየትንኩርሽታቸው ….
...
በአያገባው ነገር በሰው እየገባ
በአያገባው ነገር በሰው እየገባ
ውስጡ ባዶ ሲሆን ለራሱ እየባባ
መስመሩ ሲጠፋው የመውጫው ቀዳዳ
የውስጡ ባዶነት ሲሆንበት እዳ
ጓደኛ ምን ይሰራል ወዳጅ፣ ዘመድ፣ ወላጅ፣ … ወዘተረፈስ እኔ
ስወለድ ብቻየን እንጅ ይህ ሁሉ ግሳንግስ አብሮኝ አልመጣ፡፡ የሰው ልጅ ይኖር ዘንድ የሚያስፈልገው እነዚህ ሁሉ ገተቶች ሳይሆኑ
ገንዘቡና ገንዘቡ ብቻ ናቸው፡፡ ምንም ከነሌለው ሁሉ ይርቀዋል፡፡ ሁሉም ዝቅ አድርጎ ያየዋል፡፡ ራሱን ጥሎ ካገኘው ደግሞ እንዳይነሳ
ለማድረግ እዚያው ይደፍቀዋል፡፡ ከበለጠው ደግሞ ጠልፎ ለመጣል መንገድ እያመቻቸ የራሱን ጥሎ የተሳካለትን ጠረን ሲያሸት ይውላል፡፡
እኔስ በደከምኩ ሰዓት ማን ሊያቃናኝ መጣ እኔ ራሴ በራሴ ተፍጨርጭሬ አይደለም የራሴን እንጻ የገነባሁት ፎቁስ ቆሞ እንዲታይ የሆነው በራሴ ጥረት አይደለምን ይለፈልፋል በሄደበት ሁሉ፡፡ ማንም ሰው ሊሰማው አይፈቅድም፡፡ ጆሮውን እየሰጠው ልቡን ይነፍገዋል፡፡ ዐይኑን አውሶ አእምሮውን ይነሳዋል፡፡ በአካል አብሮት ቆሞ በመንፈስ ይርቀዋል፡፡ ይህ ሁሉ ግን ለርሱ ምኑም አይደል፡፡ የሚከታተለው ኖረ አልኖረ፣ ተሰማ አልተሰማ፣ ታየ አልታየ … ምንም ደንታ የለው፤ ብቻ ግን ሁሌም ያወራል፡፡
ጎበዝ ተማሪ ነበር አሉ፤ ጓደኞቹ መተት አሰርተውበት ነው አሉ እንዲህ የሆነው፡፡ አይደለም! አንዲት ሴት ወዳው አስደግማበት ነው ይባላል፡፡ አይደልም! ይልቅስ አንዲት ቆንጆ ሴት አፍቅሮ ሲከተላት እሷ ደግሞ ሌላ ወንድ ይዘበት ነው እንዲህ አቅሉን የሳተውም ይባላል፡፡ ሴትና ሴታሴቶች ያናቡጉታል፡፡
ድንገት ከየት መጣ ያልተባለ ጎርናና የአዛውንት መሆኑ በውል ያልለየ ድምጽ የለ የለም! በቡተሊካ ምክኛት ታስሮ ወፌ ላላ ከተገረፈ በኋላ ነው አሉ እንዲህ የሆነው ይባላል፡፡ ሌላ ደግሞ ቁጣ ይሁን ለቅሶ ለመለያት ያዳገተ ድምጽ አይደለም አባየ! እናቱና ታላቅ ወንድሙ በአንድ ቀን በጥይት ሲገደሉ አጠገባቸው ሆኖ በማየቱ ደንግጦ ነው እንዲህ የሆነው ይባላል፡፡ ከሁሉም አቅጣጫ ግምት ይሠነዘራል፡፡ ማንም ዘንድ ግን እውነተኛው ምክንያት አልተገኘም፡፡ ምናልባትም በዛ ሰው ልብ እና አእምሮ ውስጥ ታሽጋ ተቀምጣ ሊሆን ይችላል፤ እስከመጨረሻውም ሳትገለጥ ልትቀር ትችላለች፡፡
ህይወት ኡደት ነች፡፡ የደረሱበትን አልፈው ያልደረሱት ተደርሶ ተመልሶ የመጀመሪያው ስፍራ ላይ የሚታረፍባት፡፡ እንደ ፕሮፌሰሩ የመሰላል ግጥም የረገጡትን አስጨብጣ የጨበጡትን የምታስረግጥ፡፡በምብርክክ አስሂዳ በመኪና ምታንፈላስስ፡፡
ጌታ ያድናል፡፡ ሁሉም ነገር በርሱ ነው፡፡… ቅብርጥሴ፣ ይሰብኩኛል፡፡
አሜን ብያቸው አልፋለሁ፡፡
Subscribe to:
Comments (Atom)
እኔ የማወራት የእርሷ ጆሮ ሲደርስ መልኩን እየሳተ እየተቀየረ፣ ከማፋቀር ይልቅ እኛን ከማዋደድ ጥል ፈጣሪ ኾነን እያጠራጠረ፡፡
-
በድንቅ ተጋድሎ አሻራ ያኖረ፣ በሑባሬ ገመድ ሐገርን ያሰረ፡፡ ማረሻና ድግር፣ ሞፈርና ቀንበር ተሸክሞ ወጥቶ የሚታገል ካፈር ማጭድና መንሹን ማርገቢያ ላይዳ ችግሩን ሸክፎ ከትቶ በአኩፋዳ ጋራው...
-
ያለፉት ዐርባ አምስት (45) ዓመታት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በመጠላለፍና ጣት መቀሳሰር የተሞላ እንደነበርና እንደሆነ የሚያሳዩን በርካታ ማስረጃዎች አሉ፡፡ ይህም በዛሬው ትውልድ ላይ የቀረውን ጠባሳ ሰፊ እንዲሆንና ዐዲ...
-
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን የጉዞውን መነሻ በ19 ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ብቅ ባሉት ጋዜጣዎች ጀምሮ በዓይነት እና በቁጥር እየሰፋ ዛሬ ላይ ያለበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ጋዜጣ ምዕት ዓመት የሞላው ሲሆን የመጀመሪያው ሬዲ...